“የተደራጁ ወጣቶች የልማት አቅም ናቸው” !!!

የማህበሩ አመሰራረት

 
               
                 የአማራ ወጣቶች  ማህበር  አመሰራረት

የአማራ ወጣቶች ማህበር ለማናቸውም የፖለቲካም ሆነ የሀይማኖት ተቋማትና ድርጅቶች የማይወግን ፤ ነፃ ማህበር ሆኖ በሚመለከታቸዉ አካላት እዉቅናና ፈቃድ በአዋጅ ቁጥር 194 መሰረት ፤ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል በ1995 ዓ.ም የተመሠረተ ማህበር ነው።

አቶ ጋሻው አዘነ

የአማራ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

የዞን ቅርንጫፎች

አዳዲስ ዜናዎች

ወጣቶች አሁን የገጠሙንን ክልላዊ ፈተናዎች ማሻገር የሚችል እምቅ አቅም አላቸው”
“አከባቢያችንን እንጠብቃለን ሰላማችንን እናመጣለን “በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው ዕለት የእንጅባራ...
“የማኅበሩ ዓላማ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው”
“የማኅበሩ ዓላማ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው” የአማራ ወጣቶች ማኅበር ”የተደራጁ...
የአማራ ወጣቶች ማህበርን እናስተዋውቅዎ !
የአማራ ወጣቶች ማህበርን እናስተዋውቅዎ ! በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ለዉጥ እና...

የማህበሩ ፕሮግራም

ስለ ህገ-ወጥ ስደት ግንዛቤ መስጠት

ህገወጥ የሰወች ዝውውር የሚያስከትለውን ጉዳት በተመለከተ ለ10,000 ሽህ ያህል ወጣቶች ግንዛቤ መፍጠር፣ወጣቱ በሃገሩ ሰርቶ መለወጥ እንደሚችል ትምህርት መስጠት።

በግብርና እና በከትሞች በሚካሄዱ ልማታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፤ በተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራ ሁሉንም የማህበሩ አባላት በተደራጀ መንገድ ተሳታፊ ማድረግ፤በተፈጥሮ ሀብት ስራ የዳኑ እና ያገገሙ ተራሮችን መጠበቅና መንከባከብ ላይ የማህበሩ አባላት የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል።በገጠር የእርሻ መሬት ለሌላቸዉ ወጣቶች ከሚመለከትዉ አካል ጋር በመነጋገር መሬት የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸትና 20,000 የማህበሩን አባላት በመስኖ ስራ እንዲሰማሩ ማድረግ። ከቴክኒክና ሙያ ኢንተርኘራይዞች ልማት ጋርና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመነጋገር 15,000 ለሚሆኑ የከተማ የማህበሩ አባላት የስራ እድል መፍጠር፣ በማህበር ተደራጅተው ስራ በመሰራት ላይ የሚገኙ አባላትን መደገፍ፣ የብድር የመሰሪያ ቦታ ጥያቄወች ያለምንም ቢሮክራሲ ምላሽ የሚያገኙበትን መንገድ ማመቻቸት።

በየደረጃው ባሉ መዋቅራችን የፀረ-ሙስናና ስነ-ምግባር ክበባትን ማቋቋም! በብልሹ አሰራር እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ ለማህበሩ አባላት እና ለዞንና ለወረዳ አመራሮች የክልል አጋር አካላትን በማስተባበር ስለፀረ ሙስናና ብልሹ አሰራር ትግል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት።ከዚህ በተጨማሪም ከየትኛውም ፖለቲካ ፖርቲ ነፃ የሆነ አደረጃጀት በመፍጠር በቀጣይ 2018 ዓ.ም የሚካሄደዉን 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በክልላችን በሁሉም አካባቢዎችና በአዲስ አበባ

ስለ አደገኛ መድሀኒቶች እና እፆች ጐጅነት እንዲሁም ይህን ተከትለው ስለሚመጡ እንደ ኤች አይ ቪ እና መሰል የጤና ቺግሮች ለአባላት እና 500,000 ለሚሆኑ ወጣቶች ግንዛቤ መፍጠር፤ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመተባበር ወጣቶች ነጻ የትምህርት እድል እንዲአገኙ ማስቻል፤የወጣት ማዐከላት እንዲገነቡ፡ከዚህ በፊት የተገነቡትንም ማጠናከር እና ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል።

አጋሮቻችን

ያግኙን

Scroll to Top