“የተደራጁ ወጣቶች የሰላም፣የዲሞክራሲና የልማት አቅም ናቸው” አወማ !!

የማህበሩ አመሰራረት

 

የአማራ ወጣቶች ማህበር ለማናቸውም የፖለቲካም ሆነ የሀይማኖት ተቋማትና ድርጅቶች የማይወግን ፤ ነፃ ማህበር ሆኖ በሚመለከታቸዉ አካላት እዉቅናና ፈቃድ በአዋጅ ቁጥር 194 መሰረት ፤ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል በ1995 ዓ.ም የተመሠረተ ማህበር ነው።

ወጣት ጋሻው አዘነ ሙሉ

የአማራ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

የዞን ቅርንጫፎች

አዳዲስ ዜናዎች

Just before claiming any render, it�s vital to feedback the
By far the most rewarding no-deposit Dude Spin Casino på...
These give over 100 posts to your account access, campaigns,
Make sure to gamble responsibly-place limits, bring breaks, and concentrate...
The latest put fits offers an excellent fourteen-big date authenticity
Some of the issues i discover could be the volatility...

የማህበሩ ፕሮግራም

ስለ ህገ-ወጥ ስደት ግንዛቤ መስጠት

ህገወጥ የሰወች ዝውውር የሚያስከትለውን ጉዳት በተመለከተ ለ10,000 ሽህ ያህል ወጣቶች ግንዛቤ መፍጠር፣ወጣቱ በሃገሩ ሰርቶ መለወጥ እንደሚችል ትምህርት መስጠት።

በግብርና እና በከትሞች በሚካሄዱ ልማታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፤ በተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራ ሁሉንም የማህበሩ አባላት በተደራጀ መንገድ ተሳታፊ ማድረግ፤በተፈጥሮ ሀብት ስራ የዳኑ እና ያገገሙ ተራሮችን መጠበቅና መንከባከብ ላይ የማህበሩ አባላት የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል።በገጠር የእርሻ መሬት ለሌላቸዉ ወጣቶች ከሚመለከትዉ አካል ጋር በመነጋገር መሬት የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸትና 20,000 የማህበሩን አባላት በመስኖ ስራ እንዲሰማሩ ማድረግ። ከቴክኒክና ሙያ ኢንተርኘራይዞች ልማት ጋርና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በመነጋገር 15,000 ለሚሆኑ የከተማ የማህበሩ አባላት የስራ እድል መፍጠር፣ በማህበር ተደራጅተው ስራ በመሰራት ላይ የሚገኙ አባላትን መደገፍ፣ የብድር የመሰሪያ ቦታ ጥያቄወች ያለምንም ቢሮክራሲ ምላሽ የሚያገኙበትን መንገድ ማመቻቸት።

በየደረጃው ባሉ መዋቅራችን የፀረ-ሙስናና ስነ-ምግባር ክበባትን ማቋቋም! በብልሹ አሰራር እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ ለማህበሩ አባላት እና ለዞንና ለወረዳ አመራሮች የክልል አጋር አካላትን በማስተባበር ስለፀረ ሙስናና ብልሹ አሰራር ትግል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት።ከዚህ በተጨማሪም ከየትኛውም ፖለቲካ ፖርቲ ነፃ የሆነ አደረጃጀት በመፍጠር በቀጣይ 2018 ዓ.ም የሚካሄደዉን 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በክልላችን በሁሉም አካባቢዎችና በአዲስ አበባ

ስለ አደገኛ መድሀኒቶች እና እፆች ጐጅነት እንዲሁም ይህን ተከትለው ስለሚመጡ እንደ ኤች አይ ቪ እና መሰል የጤና ቺግሮች ለአባላት እና 500,000 ለሚሆኑ ወጣቶች ግንዛቤ መፍጠር፤ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመተባበር ወጣቶች ነጻ የትምህርት እድል እንዲአገኙ ማስቻል፤የወጣት ማዐከላት እንዲገነቡ፡ከዚህ በፊት የተገነቡትንም ማጠናከር እና ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል።

አጋሮቻችን

ያግኙን

Scroll to Top